• Skip to main content
  • Skip to primary sidebar

Africa Horn Now

"We don't take sides; we help you see more sides."

Africa Horn Now

ካብ ውሽጢ ቤት ማእሰርታት ኤርትራ

Published: May 6, 2021

PBS: Escaping Eritrea … [Read More...] about ካብ ውሽጢ ቤት ማእሰርታት ኤርትራ

አገሪቷ ወደ ብተና ማምራቷ አይቀርም – አቶ ስብሃት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ

January 4, 2017 By Africa Horn Now

አርአያ ጌታቸው | January 3, 2017 | zehabesha

የኢህአዴግ ጉባኤ አሰራሩ መፈተሽ እንዳለበት አቶ ስብሃት ነጋ አመለከቱ
ኢህአዴግ ሙሰኞችን ካልከሰሰ አገሪቷ ወደ ብተና ማምራቷ አይቀርም ብለዋል

የኢህአዴግ ጉባኤ አሰራሩ የብሄራዊ ድርጅቶችን ወቅታዊና ትክክለኛ አቋም የሚያሳይ ነው ብለው እንደማያምኑና መፈተሽ እንዳለበት አንጋፋው የኢህአዴግ ታጋይ/የህወሓት መስራች/ አቶ ስብሃት ነጋ ተናገሩ፡፡ ኢህአዴግ ባመነው ልክ ሙሰኞችን ካልከሰሰ አገሪቷ ወደ ብተና ማምራቷ አይቀርም ብለዋል፡፡

አቶ ስብሃት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ብቻ በሰጡት ቃለ መጠይቅ እንደተናገሩት፤ የኢህአዴግ ጉባኤ አካሄዱ ተቻችሎ የማለፍ፣ ህዝባዊነት የተሸረሸረበትና ነገሮችን አስቀድሞ ያለማየት ችግር ያለበት በመሆኑ አካሄዱ በጥልቀት መፈተሽ አለበት የሚል እምነት አላቸው፡፡

እንደ አቶ ስብሀት ገለጻም፤ በጉባኤው ዋዜማ ህዝቡና አባሉ በአጀንዳዎቹ ላይ የሚወያይበት፣ ጉባኤተኛው አመራሩን በጥልቀት የሚያውቅበት፣ የአስር እና ሃያ አመት ፖሊሲና ስትራቴጂ የሚወጣበትና አርቆ የሚያይ ጉባኤ ቢሆን ምኞታቸው ነው፡፡ ወደፊትም የዚህን አይነት አካሄድ ይከተላል የሚል ግምት አላቸው፡፡

በጉባኤው ላይ ብሄራዊ ድርጅቶቹ ያሉበትን ትክክለኛ ገፅታ አያቀርቡም፤ ቢያቀርቡ ኖሮማ 10ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ በተካሄደ በወራት ውስጥ በአማራም ይሁን በኦሮሚያ የተከሰተው ችግር ባልተፈጠረ ነበር በሚል ትችት የሚያቀርቡ አካላት አሉ፤ ተብለው የተጠየቁት አቶ ስብሃት በምላሻቸው፤ “የእኔም ድምዳሜ እንደዚያ ነው፤ ጉባኤተኛው ያለበትን ችግር አምኖ የሚመጣና ጉባኤውን መደምደሚያ ማድረግ ነው ያለበት፡፡ እያንዳንዱ ድርጅት በራሱ በሚያካሂደው ጉባኤ ላይም እንደ ኢትዮጵያ አንድ ላይ ለመቀጠል የሚያስቸግር የአመለካከት ችግር አለብን ብሎ ያለ ምህረት ተገማግሞ ሲያበቃ ነው ወደ ድርጅቱ አጠቃላይ ጉባኤ መምጣት ያለበት፡፡ ከዚህ አንጻር ያለፉት ጉባኤዎችም መገምገም አለባቸው” ብለዋል፡፡

አገሪቷ የገባችበት ወቅታዊ ችግርን በተመለከተም አቶ ስብሃት በሰጡት ማብራሪያ፤ አሁን እየታየ ያለው ችግር መንስኤው ከ15 አመት በፊት በተካሄደው ተሀድሶ አሁን ባለው ልክ ችግሮች በጥልቀት አለመፈተሻቸው፣ እጥረቶችንም አደባባይ በግልጽ አለማውጣትና ተቻችሎ የመሄድ ችግሮች ናቸው ብለዋል፡፡ ጠባብነትና ትምክህት የስርዓቱ አደጋ እንደሆኑ ከአመታት በፊት ቢለዩም በትኩረት ስላልተሰራባቸው ለተፈጠረው ሁከት ተጨማሪ ምክንያት ሆነዋል፡፡ አሁን በጥልቀት መታደስ የሚለው መፍትሄም አዋጅ ሳይሆን ሂደት በመሆኑ በዚህ ጊዜ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደማይቀመጥ ገልጸዋል፡፡

ኢህአዴግ ችግሮቹን አንድ ሁለት ብሎ ለይቶ አስቀምጧል፤ እስካሁን እግረ መንገድ ችግሮቹን ሲጠቅስ ቆይቷል እንጂ እንደ አሁኑ በጥልቀት አልለየም ነበር፡፡ በጥልቀት መታደስም ችግሩን በጥልቀት ከመረዳት ይጀምራል፡፡ የተለዩትን ችግሮችን ሳንፈታም አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ መፍጠር አይቻልም፡፡ መፍትሄው ጊዜ እንደሚፈልግ ህዝቡ መረዳትና መታገስ አለበት፤ ኢህአዴግም መፍጠንና መስራት ይኖርበታል፡፡ ይሄ ችግር በአንድ አመትና ሁለት አመት አይፈታም ብለዋል፡፡

ኢህአዴግ ለገባበት ችግር ያስቀመጠው መፍትሄ በጥልቀት መታደስ የሚልና እስከ ካቢኔን መልሶ ማዋቀር የደረሰ እርምጃ ትክክለኛ መፍትሄ ይሆናል ብለው ያምናሉ? የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ስብሀት፤ “ሰው ማስቀመጥ በራሱ ለውጥ አያመጣም፤ ማስቀመጥና በተቋሙ ተጠያቂ ማድረግ ከተቻለ ለውጥ ማምጣት ይቻላል፡፡ ለውጡ ተቋማዊ ሆኖ ተጠያቂነትና ኃላፊነት ያለበት ስርዓት ፈጥረው ይሄዳሉ ወይ? የሚለው ጥያቄ ነው፡፡ መፍትሄው ተሿሚዎቹ ወደ ተቋማቸው ሄደው በሚሰሩት ስራ ላይ ይወሰናል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

ብሄራዊ መግባባትን በተመለከተም አቶ ስብሀት፤ መግባባቱ ከአመለካከት እንደሚጀምር በመግለጽ በዚያ ደረጃ የተሰሩ ስራዎች ጠባብነትና ትምክህትን ማሸነፍ ያልቻሉ በመሆናቸው መግባባቱ ገና ቀሪ ስራ አለበት ብለዋል፡፡ የአንዱ ብሄር ባለሀብት በሌላው ብሄር አካባቢ ሄዶ ቢያለማ እንደ አካባቢው ባለሀብት እኩል ይታያል ወይ? አዎን ከሆነ ምላሹ ብሄራዊ መግባባት ተፈጥሯል ማለት እንችላለን፤ አያየውም ከሆነም አልተፈጠረም ነው ምላሹ፡፡ ምክንያቱም መግባባት በአየር ከላይ ሳይሆን በመሬት ላይ ነውና ሲሉም ተናግረዋል፡፡

ህዝቡ የሚያነሳው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሳይቀር የገለጹትን የሙስና ችግር በጅምላ “የሙስና ችግር አለ” ከማለት በዘለለ ሙሰኛው ማን እንደሆነ በግልጽ የሚነገርና የሚጠየቅ የለምና በዚህ ዙሪያ ምን አስተያየት አለዎት? ተብለው የተጠየቁት አቶ ስብሃት ሲመልሱ፤ የመንግስትን ስልጣን ለግል ጥቅም ማዋል ችግር አለ ተብሎ በግልጽ ተለይቷል፤ የተሀድሶውም አጀንዳ ሆኗል፤ ህዝቡም የሚጠብቀው ይሄንን ነው፤ ይሄ መቼና ከማን እንደሚጀምር ባላውቅም ኢህአዴግ ያጠፋውን የሚጠይቅበት፣ ተቻችሎ መሄድን የሚያቆምበት ውሳኔ ላይ መድረሱን አውቃለሁ፤ ኢህአዴግ ይሄንን በምሬት እንደሚሄድበትም እረዳለሁ፤ ካልሄደበት ደግሞ ችግሩ ይቀጥላል፤ አገርም ይፈርሳል ነው ያሉት፡፡

ኢህአዴግ በታሪኩ ካጋጠሙት ፈተናዎች ሁሉ አሁን የገባበት ችግር ከፍተኛውን ደረጃ እንደሚይዝ የተናገሩት አቶ ስብሃት፤ ከዚህ ችግር ለመውጣት ደግሞ ድርጅቱ በታሪኩ ጥልቅ በሆነ መልኩ ያሉበትን እጥረቶች ዘርዝሮ ማስቀመጡን ገልጸው፤ ያስቀመጣቸውን መፍትሄዎች አንድ ሁለት ብሎ ከፈጸማቸው በታሪኩ ከደረሰበትም በላይ ደረጃ መድረስና ይሄን አገርና ህዝብ ወደ ታላቅ ደረጃ ማድረስ ይችላል ብለዋል፡፡

ከአቶ ስብሀት ጋር ያደረግነውን ቃለ መጠይቅ ሙሉ መረጃ ሳምንት ይዘን እንቀርባለን፡፡

 

Filed Under: TIGRINJA

Primary Sidebar

A New Administration Won’t Heal American Democracy

Published: November 6, 2020

The Rot in U.S. Political Institutions Runs Deeper Than Donald Trump Larry Diamond | November 5, 2020 | Foreign … [Read More...] about A New Administration Won’t Heal American Democracy

Archives

  • May 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • July 2020
  • June 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • June 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • April 2018
  • March 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • December 2017
  • November 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • December 2016
  • November 2016
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • July 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • February 2016
  • January 2016
  • December 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • July 2015
  • June 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • March 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • July 2014
  • May 2014
  • March 2014

Log In

Copyright © 2025 Africa Horn Now · WordPress · Log in